Posts

Showing posts from April, 2018

የአብዲሳ አጋ ¬ አስገራሚ ታሪክ – የኢትዮጵያ ጀግና !!!

Image
    አብዲሳ አጋ በ1928 ዓ/ም የጣልያን ወረራ ወቅት ተማርኮ ወደ ጣልያን ከተወሰደ በኋላ ብርድ ልብሱን ቀዳዶ በመቀጣጠል በመስኮት አምልጦ በርካታ ጀግንነቶችን የፈጸመ የኢትዮጵያ ወታደር ነው።  ኮሎኔል አብዲሳ አጋ የተወለደው በ1912 ዓ.ም ፣ ወለጋ ነበር።   በ12 ዓመቱ አባቱ በንዴት ወንድማቸውን በመግደላቸው ሲታሰሩ አብዲሳ አባቱን ለማስፈታት የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን ቢያደርግም ሳይሳካ በሞት ተቀጥተዋል።  በኋላም በ14 ዓመቱ የኢትዮጵያን ጦር በመቀላቀል ሀገሩን ማገልገሉን ሀ ብሎ ጀመረ።  አብዲሳ ጦሩን ከተቀላቀለ ከሁለት አመት በኋላ የአድዋን ሽንፈት ለመበቀል የዛተው ፋሺስት ሙሶሎኒ በድጋሚ ኢትዮጵያን ሲወር ሀገሩን ለመከላከል በ16 ዓመቱ ወራሪውን ጦር መዋጋት ጀመረ። ውጊያ ላይ ባጋጠመው የመቁሰል  አደጋ ህክምና ላይ ከቆየ በኋላ አዲስ አበባ ውስጥ ፒያሳ አካባቢ በሚገኝ ቤት በቁም እስር ላይ ነበር። በኋላ ጣልያን ኢትዮጲያን እንዲያስተዳድር በሾመችው ግራዚያኒ ላይ የመግደል ሙከራ ከተደረገ በኋላ አብዲሳ አጋ እና ሌሎች 37 የሚሆኑ የቁም እስረኞች ተጠርጣሪ ተብለው በከባድ ስቃይ እስር ቤት ከቆዩ በኋላ በወቅቱ የጣልያን ግዛት በነበረችው በሶማሊያ በኩል ወደ ጣልያን ተወስዶ በሲሲሊ ደሴት በሚገኝ እስር ቤት እስረኛ ተደረገ። አልሸነፍ ባይነት መለያው የሆነው አብዲሳ ሁሊዮ ከተባለ ዩጎዝላቪያዊ የጦር እስረኛ ጋር በመተባበር ከባድ ጥበቃ ከሚደረግበት እስር ቤት ለማምለጥ ማሰላሰል ጀመረ። ተሳክቶለት ቢያመልጥ እንግዳ አገር እንደሚጠብቀው ቢያውቅም በነጻነቱ የማይደራደረው አብዲሳ የተሰጠውን የብርድ-ልብስ ቀዳዶ በመቀጣጠል በመስኮት በኩል አመለጠ። ከዛ በኋ...

እያዩ ይናገራል...

Image
እረፉ ! “ ዘመመ !” ብላችሁ የሰው ቤት አትግፉ እሾህ ለማሳመር አበባ አታርግፉ። እረፍ ! “ ቆሜያለሁ !” ለማለት አጥሬን አትደገፍ ለአመዳም ወዘናህ ቆዳዬን አትግፈፍ። እረፍ ! በመስመርህ ፍካ በድንበርህ ለምልም በየአልጋህ እደር በየእንቅልፍህ አልም። እረፊ ! በኩረጃ ንባብ ትርጉም አትግደፊ በሰባራ መርፌሽ የሰው ልክ አትስፊ። . . . . ማን አንደጠለፈኝ ማን እንደሰበረኝ ጠያቂ አጣሁ እንጂ መልስማ ነበረኝ። ምክንያት ታመመ መፍትሄ ታመመ ከጥያቄው በፊት መልሱ እየቀደመ። ሌብነት ገነነ ግርግር ገነነ ብልጭልጭ ገነነ ድንግርግር ገነነ ኪሳራ ገነነ ደላሎች ገነኑ፣ ደላሎች ጀገኑ ባልዋለ ገበያ ዋጋ እየተመኑ !!!!! " ፊት ፊቷን ብታይ ጠሪዋ በዛ ለስንቱ ትዙር አንድ አንገት ይዛ " *** " የማንም ቆራጭ መጥረቢያ ቢስል እዬዬ አልልም እንጨት ይመስል " ፡ መሸነፍ ደስ የሚለው ደና አሸናፊ ሲገኝ ነው !!!